=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=
ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ
1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።
2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።
3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።
4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
![]() =<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=
![]() በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። ![]() |
---|
ምን ያማረ ስም ነው ጣፋጭ
ይዞጭልጥ የሚል ልብ መሳጭ
በአንተነትህ የተጥራራህ
ከፍጥረታት የተብቃቃህ
ሰማይና ምድርን የዘረጋህ
ምስጋና ሁሉ የሚገባህ
አጋዥ የለህ አማካሪ
ያሻህን ሁሉ ሰሪ
አስተካካይ አሳማሪ
ራስህን የቻልክ ተብቃቂ
ይፋ ድብቅ ሁሉ አዋቂ
ህይወት ሰጭ ጥበበኛ
ስለእውነት ፈራጅ ዳኛ
ምን እናድርግ የኔ ጌታ
ምን እንፍጠር መላ እንምታ?
ምን እናውጣ ምን እናውርድ?
ምን እንምከር ምን እንዘይድ?
እንድንወጣ ከማዕበሉ
ከዱንያ ውሽንፍሩ
ከድቅድቁ ከጨለማው
ከነገሰው ካንሰራፋው
ምን እናድርግ ያረህማኑ
እንዲደርሰን ብርሃኑ
እንዲታየን ጭላንጭሉ
የእምነት ብርሃን ወጋግኑ
ምን እናድርግ የኔ ጐታ?
ምን እንፍጠር መላ እንምታ?
የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ |
---|